ክስተቶች

ክስተቶች Event

image description
የመጀመሪያ ቀን icon
የመጨረሻ ቀን icon
አካባቢ የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ

ችግኝ እንተክላለን፤ ተንከባከብንም የጽድቀት መጠኑን እናሳድጋለን" (የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ አመራርና ሠራተኞች) 

መስከረም 10/2018 (መልአ) 

በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ አመራርና ሠራተኞች "ችግኝ እንተክላለን፤ ተንከባከብንም የጽድቀት መጠኑን እናሳድጋለን" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ኩትኳቶና እንክብካቤ አደረገዋል። 

የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ወንዶሰን ባንጃው በአገራችን የታሠበውን የአረንጓዴ አሻራ ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን አድገው ለፍሬ እንዲበቁ ልንከባከባቸው ይገባል ብለዋል። 

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ እንደ ሀገር  ተግባራዊ እየሆነ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መረሀ ግብር በመሳተፍ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የጽድቀት መጠናቸውን ለማሳደግ የመንከባከቡን ተግባር ከማዕከል እስከ ቅርንጫፍ ጽቤቶቸ እያከናወነ ይገኛል።

  • icon 9:30am - 1:00pm
  • የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ

Related Events