የመጀመሪያ ቀን
icon
የመጨረሻ ቀን
icon
አካባቢ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ
value="
በዘጠኝ ክፍለ ከተሞች 220 ፕሎቶች የተሰናዱበት 8 ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ሰነድ ሽያጩ ከታህሳስ 25/2018 ጀምሮ በኦንላይን እየተካሄደ ይገኛል።
የሰነድ ሽያጩ ጥር 26/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ድረስ ብቻ በመሆኑ የቀሩት ቀናት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው።
ስለሆነም በዚህ ግልጽና ነፃ በሆነው የመሬት ሊዝ ጨረታ መሳተፍ ካሰቡ ለጨረታ የተሰናዱ ቦታዎችን በየ ክፍለ ከተማው ጠዋት 3:00 ሰዓት ከሰዓት 8:00 ሰዓት በአካል ተገኝተው ማየትና መወዳደር ይችላሉ።
ይህን ስንሎ በተለያዩ ማህበራዊ ገፆች በዚህ ዙር ለጨረታ ያልቀረቡና ህጋዊነት የሌላቸው ቦታዎችን ለጨረታ እንደቀረበ ተደርጎ ሲዘዋወር ተመልክተናል።
ስለሆነም በክፍለ ከተማው ከተመደቡ ባለሙያዎች ውጭ በምንም መልኩ ለጨረታ የቀረቡ ቦታዎች ምልከታ( ጉብኝት) እንደማይደረግ አውቀው ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው ያሳስባል።
"